ሊግ ስፖርትን በቅዳሜ እትም
ተወዳጇ ጋዜጣዎ ሊግ ስፖርት ነገ ለንባብ ትቀርባለች፤
በዕለተ ቀኗ ምን ምን ጉዳዮችን ይዛ ታስነብቦት ይሆን?
በሀገር ውስጥ ዘገባዋ ቤትኪንግ ፕሪምየር ሊጉን አስመልክቶ ውድድሩን ከሚመራው ወላይታ ድቻ ተጨዋቾች ውስጥ በተከታታይ ግጥሚያ ላይ ግብን እያስቆጠረ የሚገኘው ቃለኪዳን ዘላለም ስለ ቡድኑና ስለ ራሱ ይናገራል፡፡ የቀድሞ ክለቡ ቡና ላይ የድል ግብን ማስቆጠሩን ተከትሎም ያለው ይኖራል፡፡
ሊግ በሌላ ሀገር ውስጥ ዘገባዋ የወልቂጤ ከተማው አጥቂ ጌታነህ ከበደም ጋር ቆይታ አላት፡፡ ጌታነህ በአሁን ሰዓት ላይ እያስመዘገቡት ያለው ውጤት ጥሩ መሆኑንገልፆ ከፊርማ ክፍያ ጋር በተያያዘ ደግሞ የቡድናቸው አብዛኛዎቹ ተጨዋቾች ልምምድ ማቆማቸው ደግሞ በቀጣይነት የሚኖራቸው ውጤት ላይ ስጋት ሊፈጥርባቸው እንደሚችል ይናገራል፡፡
ሊግ ስፖርት በባህር ማዶ ዘገባዋስ የተለያዩ ሊጎች ዘገባዎችንና ማራኪ የሆኑ የተጨዋቾች ግለ ታሪክንም ታስኮመኩሞታለች፡፡
ሊግ አታምልጦት፤ የእርስዎ ናት፡፡
የነገ እትም የፊት ለፊት ምስሏም ይሄንን ይመስላል፡፡
ሊግ ስፖርትን በቅዳሜ እትም ተወዳጇ ጋዜጣዎ ሊግ ስፖርት ነገ ለንባብ ትቀርባለች፤ በዕለተ ቀኗ ምን ምን ጉዳዮችን ይዛ ታስነብቦት ይሆን?
ተመሳሳይ ጽሁፎች