Free Porn
xbporn

buy twitter followers
uk escorts escort
liverpool escort
buy instagram followers
6x games unblocked fnaf unblocked games 76 unblocked games krunker.io slither unblocked io premium unblocked github.io unblocked games
Google search engine

“ከእዚህ በኋላ ባለመሸነፍ ሪከርድ ለመጓዝና ሻምፒዮና ለመሆን ተዘጋጅተናል” “የኢትዮጵያ ቡናና የቅ/ጊዮርጊስን በሚያስታውሰን የደርቢ ጨዋታ ባህርዳርን ባለማሸነፋችን ተከፍተናል” ታፈሰ ሰለሞን /ፋሲል ከነማ/

“ፋሲል ከነማ የመጀመሪያውን ጨዋታ ቱኒዚያ ላይ አድርጎ ቢሆን ኖሮ ረጅም ጉዞን ይጓዝ ነበር”

“በፋሲል ከነማ  ቆይታዬ  አሁንም ምርጡን ብቃቴን ማሳየቴን እቀጥላለሁ”

ታፈሰ ሰለሞን /ፋሲል ከነማ/

በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የተጨዋችነት ዘመን ቆይታው ድንቅ ብቃቱን በሜዳ ላይ ማሳየት ችሏል፤ በችሎታውም ብዙዎቹ  ያደንቁታል።

ለልደታው ኒያላ ክለብ ጀምሮ ለኢትዮ- ኤሌክትሪክ፣ ለሐዋሳ ከተማና  ለኢትዮጵያ ቡና ሲጫወትም የሚያሳየው ጥሩ ብቃት ለብሄራዊ ቡድን እስከመጠራት ደረጃም  ላይ ያደረሰው ሲሆን ለዋልያዎቹ የተጫወተበት አጋጣሚም ይታወሳል።  አሁን ደግሞ በክረምቱ ወራት የተጨዋቾች ዝውውር መስኮት ከኢትዮጵያ ቡና ጋር መለያየቱን ተከትሎ ለፋሲል ከነማ በመፈረም ቡድኑን በጥሩ ሁኔታ እያገለገለም ይገኛል።

የፋሲል ከነማ  የአማካይ ስፍራ ተጨዋቹ ታፈሰ ሰለሞን በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የቡድናቸው ተሳትፎ ዙሪያ፣ በኢትዮጵያ ቡና ስለነበረው ቆይታና ከክለቡ ጋር ስለመለያየቱ እንደዚሁም ደግሞ ከራሱ ብቃት ጋር በተያያዘ እና በሌሎችም ተያያዥ በሆኑ ጉዳዮች ላይ የሊግ ስፖርቱ ጋዜጠኛ መሸሻ ወልዴ /G.BOYS/ አነጋግሮት የሚከተሉትን ምላሾች ሊሰጠን ችሏል፤ ተከታተሉት።

ሊግ፦ በቅድሚያ ለቃለ-ምልልሱ ፈቃደኛ በመሆንህ እናመሰግንሃለን?

ታፈሰ፦ እኔም የጋዜጣችሁ እንግዳ አድርጋችሁ ስለጋበዛችሁኝ ከልብ ላመሰግናችሁ እወዳለሁ።

ሊግ፦ በክረምቱ የተጨዋቾች ዝውውር መስኮት ወደ ፋሲል ከነማ በማምራት ለክለቡ እየተጫወትክ ይገኛል፤። ወደ ቡድኑ ስታመራ ፋሲል የመጀመሪያ ምርጫህ ነበር?

ታፈሰ፦  አዎን፤ በእርግጥ ሌሎች ክለቦችም ጥያቄዎችን አቅርበውልኝ ነበር። ያም ሆኖ ግን እኔ ለፋሲሎች መጫወትን የቅድሚያዬ ምርጫ ስላደረግኩኝ ወደ እነሱ ልጓዝ ችያለሁ።

ሊግ፦ ፋሲል ከነማ ከእዚህ ቀደምስ ጥሪ አቅርቦልህ ያውቃል?

ታፈሰ፦ ከአንዴም ሁለት ጊዜ ነዋ! በአሰልጣኝ ውበቱ አባተ የሀላፊነት ጊዜና በስዩም ከበደ የሀላፊነት ጊዜ ጥሪዎችን ቢያደርጉልኝም በቡና ቆይታዬ ውሌን ከማራዘም ጋር በተያያዘ ወደ  እነሱ ሳላመራ ቀርቻለሁ።

ሊግ፦ በኢትዮጵያ ቡና ያሳለፍከው የኳስ ጊዜ እንዴት እና በምን መልኩ ይገለፃል? ከክለቡ ጋር የመለያየታችሁ ዋንኛው ምክንያትስ ምን ነበር?

ታፈሰ፦ ወደ ቡድኑ የገባሁበት እና አቡበከር ናስርም የሊጉ ኮከብ ግብ አግቢ በተባለበት ዘመን ላይ ምርጥ እና ጥሩ ጊዜን ነበር ለማሳለፍ የቻልኩት። ከእዛ በኋላ በነበረው ዓመት ላይ ግን ከቡድኑ ጋር ደስተኛ አልነበርኩም። የእዛ ዋናው ምክንያትም  የክለቡ አመራሮች ደስ የማይል ነገርን ያደርጉ ስለነበርና ከውጤትም ለመራቅ ስለቻልን ከእዛ ውጪም በተጨዋቾችና በእነሱ  አካባቢም መስማማቶች ስላልነበሩ  ከቡድኑ እንዲለቁኝ ጥያቄ ባቀርብም መልቀቅ እንደማይፈልጉ ነግረውኝ ወደ ቡድኑ ብመለስም የውድድር ዘመኑ ሲያልቅ ብዙ ተጨዋቾች እንደሚለቁ በማወቄና ከእነሱ መካከልም አንዱ እኔ ስለሆንኩኝ ከቡና ጋር በእዚህ መልኩ ለመለያየት ችያለሁ።

ሊግ፦ ከኢትዮጵያ ቡና ለመለያየትህ የክለቡን አመራሮች ምክንያት አድርገሃል፤ ራስህ ጋርስ ችግር የለም?

ታፈሰ፦ ችግሮችማ ይኖራሉ፤ ግን  ስትቀጣ ተጨዋችን እስከማጥፋትና እስከ መግደል ደረጃ የሚደረስ ከሆነ ከባድ ነው። ምክንያቱም ቅጣት ሲጣልብህ ቅጣቱ አንዳንዴ ማስተማሪያ ነው ሊሆን የሚገባው።  ያ በእኔ ላይ አልሰራም ሲቀጡኝ ያለ ደመወዝ ለስድስት ወር ያህል ነበር ስጫወት የነበርኩት። ቅጣት ተጨዋችን አስተምሮ የሚያልፍና ከእዛ ቅጣትም ተምሮ ክለቡን የሚጠቅምም መሆን ነው ያለበት እነሱ ያደረጉት ግን እልህ በሚመስል መልኩ ተጨዋቹ እንዳይነሳ ነው ሲያደርጉ የነበሩት።

ሊግ፦ ኢትዮጵያ ቡና ካቻምና ጥሩ የሚባል ውጤትን አምጥቷል፤ ዓምና ደግሞ በታሰበው መልኩ ቡድኑ አልተጓዘምና  ጥሩ ከነበራችሁበት ዓመት ተነስተህ ስለ ውጤት ማጣታችሁ ችግር ምን ትላለህ?

ታፈሰ፦ አንደኛ ካቻምና  አቡበከር የጎል ሪከርድ በሰበረበት ዓመት ላይ ውጤት ለማምጣት የቻልነው ቡድናችን አንድ ስለነበር ነው። ቡናን ቡና ያስባልንበት ዓመትም ነው። በራሳችን ጥቃቅን ችግሮች ካልሆነ በስተቀር ብዙ ነጥቦችን አንጥልም ነበር። የአሸናፊነት መንፈሳችንሞ አሪፍ ነበር። ከአመራሮቹና ከኮቺንግ ስታፉም ጋር መልካምና ጥሩ ግንኙነትም ነበረን። ያ ካለፈ በኋላ ግን አምና ላይ የክለቡ አመራሮች አሰልጣኙን ሊያሰሩት ስላልቻሉ እና የተጨዋች ግዢም ላይ ብዙም ተሳትፎ ስላላደረጉለትና እሱን ለማበረርም የተደረጉ ነገሮች አሉም ብዬ  ስለማስብ ከእዛ ውጪም ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፍ እየቻልን ከኢንተርናሽናል ጨዋታ የወጣንበት መንገድም አሁን ድረስ ለእኔ ስለማይዋጥልኝ ሌላው ደግሞ ውጤትን አጥብቀው የሚፈልጉት የደጋፊዎቻችን ስሜት ጥሩ ሆኖ ሳለ በሚሰሩት ስራ ግን ደስተኛ ስላልነበርኩ ይኸውም ድንገት ከመሬት ተነስተው ተጨዋችን ይቀጡ ስለነበርም ለምሳሌ ሚኪን ማንሳት ይቻላል ሚኪያስ ለቡድኑ ሲጫወት ነው የተጎዳው፤ ተጎድቶ የአራት ወር ደመወዙን ተቀጥቷል። ጉዳት ላይ ያለን ተጨዋች እየቀጣህ እንዴት ነው ነገ ከጉዳቱ አገግሞ የሚጫወተውና   ሙሉ ለሙሉ በአመራሮች ችግር ነው ኮቺንግ ስታፉንና ተጨዋቹን አላሰራ ስላሉ ውጤትን ልናጣ የቻልነው፤ በተለይም ደግሞ ካሳዬ ብዙ መስራት እየቻለ እንዳይሰራም አድርገውታልና በመጨረሻም ከእነሱ ጋር ተለያየ።

ሊግ፦ ኢትዮጵያ ቡና የተጨዋች ጥራት ችግርም ነበረበት?

ታፈሰ፦ አዎን፤ እሱ እንዳለ ሆኖ  አላሰራም ያሉት ነገር በጣም ይገርም ነበር። ቡና አሁን ላይ የገዛቸውን ተጨዋቾች አይተሃል። ይሄን ግዢ ለእሱ አድርገውለት ቢሆን ኖሮ በእሱ አጨዋወት በእርግጠኝነት ለተከታታይ  ዓመት ሻምፒዮናም ይሆን ነበር። ካቻምና የተጨዋች ጥራት ብዙም ሳይኖር ቡድኑን እንዴት አድርጎ እንደሰራው ተመልክታቸዋልና አምና ሆን ተብሎ ነው ቡድኑ ውጤት  እንዳያመጣም ተፈልጎ በታሰበው መልኩ እንዳንጓዝ የተደረገው። በጣሞ የሚገርም ጨዋታ ሲኖር እንኳን እታች መጥተውና ወርደው አያበረታቱንም ይሄን ብዙ ጊዜ ስብሰባም ላይ ተናግሬዋለሁ። ከእዛ ውጪ አሁን እኔ የቡድኑን አንድ አንድ አመራሮች በስም ቢሮ ላይ አሉ ሲባሉ እንጂ አላውቃቸውም። አይዟችሁ የሚለን አመራርም አልነበረምና ደስ የማይል ጊዜን ነበር ያሳለፍነው።

ሊግ፦ ወደ ፋሲል ከነማ ለማምራት ችለሃል፤ የእስካሁኑ ወራቶች ቆይታህ ምን ይመስላል?

ታፈሰ፦ ፋሲል ከነማ እንደገባው በጣም ደስተኛ ነበርኩ፤ ክለቡ ትልቅ ነው፤ ምርጥ ምርጥ ተጨዋቾችም አሉበት። ከአጠገቤ ያሉ ሰዎችም ይሄን ክለብ በመቀላቀሌም ደስ ሊላቸውም ችሏል። ቡድኑን ተቀላቅዬ የመጀመሪያዬን ግጥሚያ ተቀይሬ በመግባት ሳደርግም ጎል ለማስቆጠርም የቻልኩበት ሁኔታ ስለነበር ለሌሎች ጨዋታዎችም ብርታት ሊሆነኝ ችሏል፤ በክለቡም በጣም ደስተኛም ነኝ።

ሊግ፦ የፋሲል ከነማን ሁለት ኢንተርናሽናል ግጥሚያዎች በምን መልኩ ነው የምትገልፃቸው?

ታፈሰ፦ ለውድድሩ ጥሩ ዝግጅትን ነው ስናደርግ የነበርነው። የመጀመሪያውን ጨዋታም የቡሩንዲውን ክለብ በአሳማኝ ሁኔታ አሸንፈንም ወደ ተከታዩ ዙር ልናልፍም ችለናል። ከቱኒዚያው ሴፋክሲያን ጋር በነበረን ሁለተኛው ጨዋታ ላይ ግን የሁላችንም ተጨዋቾች እምነት ነው ወደ ተከታዩ ዙር ማለፍ እየቻልን የሜዳ ላይ አድቫንቴጅን ባለመጠቀማችንና በዕጣ አወጣጡ ላይም የመጀመሪያውን ግጥሚያ  እነሱ ሀገር ላይ አድርገን ቢሆን ኖሮ  እናልፍ

 

ነበር። ግን እዚህ 0-0 በመውጣታችንና እዛ ሀገር ላይ የጎል ዕድሎችን አገኝተን ስላልተጠቀምንና 1-0 በመሸነፋችንም ልንወድቅ ችለናል። ሴፋክሲያንን እንዳየሁት ብዙም የሚከብድ ቡድን አልነበረም። ኳስ ስለሆነም ነው የተሸነፍነውና ለሚቀጥለው ጥቃቅን ችግሮቻችንን ቀርፈን መጥተን የተሻለ የሚባል ውጤትን እናመጣለን።

ሊግ፦ ከሴፋክሲያን ጋር የነበራችሁ ልዩነት ምን ነበር?

ታፈሰ፦ እንደ እኔ ምልከታ እነሱን ከሰማዋቸው ነገሮች በመነሳት መጀመሪያ ላይ በጣም አክብጄያቸው ነበር። እዚህ ሳያቸው በኳሱ ፈፅሞ አንገናኘም። እነሱ ያላቸው ነገር ሀይል ነው። አልሸነፍ ባይም ናቸው። ረጅም ኳስ ላይ አተኩረውም ነው የሚጫወቱት። ይሄን ልዩነት አይቻለው። ሜዳችን ላይ በነበረን ግጥሚያ እኛ ተጠቅመን ቢሆን ኖሮ የእነሱ ሜዳ ጥሩና አየሩም የሚከብድ ስላልነበር ማለፍ እንችል ነበር። ከእነሱ ሌላ የተመለከትኩት ነገር ቢኖር ደጋፊዎቻቸው ሲደግፉ ለደቂቃ አያርፉም። 90 ደቂቃውን ሲደግፏቸውም ነው የቆዩት። ከእኛ የተሻለ ነገር ብዙም የላቸውም።

ሊግ፦ የፋሲል ከነማ የሊግ ጉዞ እንዴት ይገለፃል?

ታፈሰ፦ እስካሁን በአራት ጨዋታ ሰባት ነጥብ ነው የያዝነው። በመጀመሪያው ግጥሚያ አዳማን ካሸነፍን በኋላ ወደ ኢንተርናሽናል ጨዋታ ነበር ለማምራት የቻልነው። ስንመለስ ከምነግርህ በላይ በጣም ድካም ስለነበረብን በመከላከያ በመሸነፍ ነጥብ ልናጣ ችለናል። በተከታታይ ቀናት እንቅልፍ ያጡ ልጆች ነበሩ። ኤርፖርት እያደርንና የመኪና ጉዞም ስለነበር ሀይል ማጣታችንም ዋጋ ሊያስከፍለን ችሏል። በኋላ ላይ ግን ራሳችን ከድካም ስሜቱ ልናገግም በመቻላችን ቅ/ጊዮርጊስን ለማሸነፍ ቻልን። በመቀጠል ደግሞ ባህርዳርን ስንገጥም ማሸነፍ እየቻልን በራሳችን ስህተት ነው ነጥብ ለመጣል የቻልነው።

ሊግ፦ ፋሲል ከነማ እንዴት የሚገለፅ ቡድን ነው፤ በዘንድሮ ውድድር ምን ውጤትን ማምጣትስ አለማችሁ?

ታፈሰ፦ ቆንጆ ቡድን ነው ያለን። በቀጣይነት ድሬ ላይ በሚኖረን ውድድርም ግጥሚያዎቹን በድል እየተወጣን ወደ መሪነቱ ስፍራ እናመራለን። በውድድር ዘመኑም ከእዚህ በኋላ ባለመሸነፍ ሪከርድ በመጓዝ የእዚህ ዓመት ዋንጫንም ከፍ አድርገን ማንሳትን ነው ግባችን ያደረግነው።

ሊግ፦ ቅ/ጊዮርጊስን በአንተ ግብ በረታችሁበት ጨዋታ ደስታችሁ ልዩ ነበር?

ታፈሰ፦ አዎን። ያ የሆነው ነጥብ ጥለን ስለመጣን ነበር። ቅ/ጊዮርጊሶች ደግሞ በተከታታይ አራት ጨዋታዎች አሸንፈው ስለነበሩና መሪም ስለነበሩ እኛ ላይ ጫናው ኖሮብን በልጆቻችን ወኔና ቁርጠኝነት ተጫውተን ስላሸነፍን ነው የተደሰትነው።

ሊግ፦ በእዛን እለት ጨዋታ ቅ/ጊዮርጊሶችን እንዴት ተመለከትካቸው?

ታፈሰ፦ እነሱ ለግጥሚያው በተለየ መልኩ ነበር የቀረቡት። እንደተጀመረ ወደፊት ጫና ፈጥረው ሲጫወቱ ነበር። ኳስ መስርተዉ ለመውጣትም ሲሞክሩ ነበር። ጥሩ ነበሩ፤ ቡና እያለው አውቃቸው ስለነበር እንደጠበቅኳቸውም አይደለም ያገኘዋቸው፤ የገጠምነውም ጥሩ የሆነውን ቅ/ጊዮርጊስንም ነው።

ሊግ፦ ከባህርዳር ከተማ ጋር ስለነበራችሁ ደርቢ ጨዋታ ምን አልክ?

ታፈሰ፦ የሁለታችን ፍልሚያ የኢትዮጵያ ቡናንና የቅ/ጊዮርጊስን የደርቢ ጨዋታ የሚያስታውሰን ነው። ህዝቡ ስታድየሙን  ሞልቶ ነበር ክለቦቹን ሲደግፍ የነበረውና ጥሩ ፉክክር በተደረገበት ጨዋታ እኛ ማሸነፍ እየቻልን አቻ ልንወጣ ችለናል፤ በመጣው ውጤትም ተከፍተናል።

ሊግ፦ በፋሲል ከነማ አሁን ላይ በምርጥ አቋምህ ላይ ነው የምትገኘው?

ታፈሰ፦ ኢትዮጵያ ቡና ሳለው ጎል ብዙም አላገባም ነበር። አሁን ላይ ግን በፋሲል ጎሎች እያገባው ነው። ቶሎ ቶሎም ጎል ጋር እየደረስኩ ነውና ለውጥ አለኝ። አሰልጣኞቹም በስራዬ እያገዙኝም ነውና በምርጥ አቋሜ ላይ የምገኝበት ወቅት ሩቅ አይደለም።

spot_img
ተመሳሳይ ጽሁፎች

አስተያይት ያስፍሩ

እባክዎን አስተያይትዎን ያስፍሩ
እባክዎን ስምዎን እዚህ ያስገቡ

ትኩስ ዜናዎች

P