Free Porn
xbporn

buy twitter followers
uk escorts escort
liverpool escort
buy instagram followers
6x games unblocked fnaf unblocked games 76 unblocked games krunker.io slither unblocked io premium unblocked github.io unblocked games
Google search engine

“ወደ ቅ/ጊዮርጊስ ያመራሁት ዋንጫን ፈልጌ ነበር” “ቤትኪንጉ ላይ ጥሩ ተንቀሳቅሻለሁ፤ የኮከብ ተጨዋችነት ሽልማቱንም እጠብቃለሁ” ጋቶች ፓኖም (ቅ/ጊዮርጊስ)

 

የቤትኪንግ ፕሪምየር ሊጉ የዓመቱ የኮከብ ተጨዋችነት ሽልማት ሐሙስ ዕለት በሸራተን አዲስ ሆቴል በተካሄደው  ፕሮግራም ላይ ይፋ ተደርጓል። በእዚሁም መሰረት ይህን ሽልማት ለማግኘት ጋቶች ፓኖም ከቅ/ጊዮርጊስ፣ ብሩክ በየነ ከሐዋሳ ከተማ እና አቡበከር ናስር ከኢትዮጵያ ቡና ለመጨረሻዎቹ ሶስት ተጨዋቾች እጩነት ቢቀርቡም ዘንድሮ የሊጉን ዋንጫ ላነሳው ቅ/ጊዮርጊስ የተጫወተውና  ለቡድኑ ጥሩ እንቅስቃሴን ያደረገው ጋቶች ፓኖም የዓመቱን የኮከብ ተጨዋችነት ክብሩን በማግኘት የ210 ሺ ብር ተሸላሚ ሆኗል።

በቤትኪንግ ፕሪምየር ሊጉ  የቅ/ጊዮርጊስ  ክለብ የመጀመሪያ  ዓመት የቡድኑ ቆይታው ላይ  ይህን የኮከብ ተጨዋችነት  ክብርን በማግኘቱ በጣም መደሰቱን ገልፆ  ይህን እንዲያሳካ ለረዱትም  ለቡድኑ አጋር ጋደኞች፣ ለኮቺንግ ስታፉ አመራሮች፣ ለቤተሰቦቹ እና ለባለቤቱና ለልጁም ምስጋናውን አቅርቧል።

በቤትኪንግ ፕሪምየር ሊጉ የዘንድሮ  የውድድር  ቆይታው  የመጀመሪያ የሊግ ዋንጫውን  ከቅ/ጊዮርጊስ ጋር  ያነሳውን ይህን የአማካይ ስፍራ ተጨዋች የሊግ ስፖርቱ ጋዜጠኛ መሸሻ ወልዴ በተለያዩ ጥያቄዎች ዙሪያ አናግሮት የሰጠውን ምላሽ በሚከተለው መልኩ አቅርበንሎታል። ተከታተሉት።

ጋቶች ፓኖም /ቅ/ጊዮርጊስ/

 

ሊግ፦ ቅ/ጊዮርጊስ  ከአምስት ዓመታት በኋላ የሊጉን ዋንጫ አንስቷል፤  በድሉ የተሰማህ ስሜት ምን ይመስላል?

ጋቶች፦ የሻምፒዮናነቱን ድል ስናሳካ በጣም ነው ደስ ያለኝ። ወደ ቡድኑ ሳመራም  ይህን ዋንጫ ከዚህ ቀደም ከሌላ ቡድን ጋር   አግኝቼ ስለማላውቅ  ወደ ቅ/ጊዮርጊስ  በማምራት ይህን እልሜን ለማሳካት ጓጉቼ ነበር። ወደ ቅ/ጊዮርጊስ ያመራሁበት ዋናው ምክንያትም ይህን ድል ፈልጌ ነበርና በመጨረሻም እልሜን አሳካሁት።

ሊግ፦ የቤትኪንግ  ፕሪምየር ሊጉን ድል ስትቀዳጁ የመጨረሻውን ቀን መጠበቅ አስፈልጓችሁ ነበር፤ የእዛን ዕለት ስለነበረው ጨዋታ እና  በሜዳው ላይና ከሜዳው  ውጪ  ስለነበረው አጠቃላይ  ድባብ  ምን የምትለው ነገር አለ?

ጋቶች፦  በቅድሚያ ወደ ጨዋታው  ሳመራ  የዕለቱን የግጥሚያ  ውጤት  ማሸነፍ መቻል  ለእኛም ሻምፒዮና የሚያደርገን ለአዲስ አበባ ከተማዎችም  ማሸነፍ መቻል ከሊጉ እንዳይወርዱ ስለሚያደርጋቸው   በጣም ደስ የሚልና ጥሩ ፉክክር የተደረገበት ጨዋታ  ነበር፤  ግጥሚያው እንደተጀመረም  አዲስ አበባ ከተማዎች እኛን አስቸግረውን ነበር። የተሻለ ለመንቀሳቀስም ችለዋል። ያም ሆኖ ግን የእኛ ቡድን የመጀመሪያውን ግብ ሲያስቆጥር  ወደ መነሳሳቱ ለመምጣት ቻለ።  ከደቂቃዎች ወደ ደቂቃዎች ባመራ ሰዓት እና  በሁለተኛው አጋማሽ ላይም የፍፁም ቅጣት ምቱን ካስቆጠረ በኋላ የበለጠ የራስ መተማመኑን ለማጎልበት ቻለ፤ በኋላ  ላይ ሌሎችን ተከታታይ ግቦች  ማስቆጠር ሲጀምር በመጨረሻ  ከእነሱ የተሻለ ሆኖ በመገኘት ግጥሚያውን በሰፊ የግብ ልዩነት ሊያሸንፍ ችሏል።  በእዚያን ዕለት ስለነበረው የሜዳውና ከሜዳው ውጪ ስለነበረውጰ ድባብ ደግሞ መናገር የምፈልገው ቅ/ጊዮርጊስ ይህን ዋንጫ ካጣ አራት ዓመታት ያለፈው ስለሆነና ደጋፊው እና የቡድኑ ተጨዋቾችም ይህን ስኬት አጥብቀው የሚፈልጉት ስለሆነ  ድጋፋቸውን በደማቅ ሁኔታ መስጠት የግድ ብሏቸው ነበር ሲያበረታቱንና  የባህርዳር ከተማ ስታዲየምን እና ከተማዋንም ሊያደምቋት የቻሉት እና  በዕለቱ የነበረው አጠቃላይ  ድባቡጰ በጣም ደስ ይላል።

ሊግ፦ ለቅ/ጊዮርጊስ  የቤትኪንግ ፕሪምየር ሊግ ሻምፒዮና መሆን በዋናነት የረዳው ነገር ምንድን ነው ትላለህ?

ጋቶች፦ የእኛ ቡድን የሊጉ ሻምፒዮና የሆነው  ዓመቱን ሙሉ በነበረው አንድነቱ፣ ህብረቱ እና በስነ-ልቦናው ደግሞ ጠንካራ ሆኖ በመገኘቱ ነው። ከእዛ ውጪ ደጋፊዎቻችንሞ በየሜዳው በመገኘት ይሰጡን የነበረው ድጋፍም በጣሙን ያነቃቃን  ስለነበር  የእነዚህ የድምር ውጤቶችም ነው ባለድል ያደረገን።

ሊግ፦ የቤትኪንግ ፕሪምየር ሊጉን ዋንጫ በመጨረሻው ቀን ላይ  ስታነሱ ተጋጣሚያችሁ ስለነበረው የአዲስ አበባ ከተማ ቡድንስ ምን የምትለው ነገር አለ?

ጋቶች፦ አዲስ አበባ ከተማዎች በእኛ ይሸነፉ እንጂ ዘንድሮ ሊጉን ዳግም እንደመቀላቀላቸው  በጣም ጥሩ ቡድን ነው ይዘው  የቀረቡት።  ጨዋታው እንደተጀመረም ፈትነውን ነበር።  በእዚህ ዓመት በሊጉ ጥሩ ከሚባሉት ቡድኖች መካከልም አንዱ ነበሩ። ወደ ታችኛው ሊግ መውረድም  አይገባቸውም ነበር።

ሊግ፦ በቤትኪንግ ፕሪምየር ሊግ የመጨረሻው  ቀን ጨዋታ ቅ/ጊዮርጊስ አዲስ አበባ ከተማን  በሰፋ ግብ ለማሸነፍ እንዲችል በአዲስ አበባ ከተማ ላይ የተሰጠው  የፍፁም ቅጣት ምት ተገቢ አይደለም የሚሉ አሉ፤  አዲስ አበባ ከተማዎችም ይህን የፍፁም ቅጣት ምት አያሰጥም በሚልም  ከመቃወም ባሻገር  የክስ ሪዘርቭም አስይዘዋል በእዚህ ዙሪያ የምትለው ነገር ካለ?

ጋቶች፦ አዲስ አበባ ከተማዎች  ይህን የፍፁም ቅጣት ምት  በተመለከተ የፈለጉትን ማለት ይችላሉ። ደግሞም የተሰማቸውን ማለት መብታቸው ነው። እንደ ሰበብ እንዳይቆጥሩት  እንጂ የፍፁም ቅጣት ምቱ በትክክል ያሰጣል። እኛ ደጋግመንም ፊልሙን ተመልክተነዋል። የፍፁም ቅጣት ምትን በተመለከተ ህጉ ላይ እንደሚለው ክልል ውስጥ አንድ ተጨዋች ለኳሱ ቅርብ ሆኖ የሚጠለፍ፣ የሚጎተት እንደዚሁም ደግሞ በየትኛውም እሱ ሊጠቀምበት በሚችል አጋጣሚ የሚነካ ከሆነና ጥቂት ንክኪ እንኳን ካለ የፍፁም ቅጣት ምት ያሰጣል ነው የሚለው። እኛም ከእነዚህ ህጎች በአንዱ ተጠቅመንም ነው የፍፁም ቅጣት ምቱን ያገኘነው፣ ጨዋታውን  ያሸነፍነውና ሻምፒዮና የሆንነው እንጂ  በእዚህ የፍፁም ቅጣት ምት ግብ ብቻ አይደለም ውጤታማ የሆነው።

ሊግ፦ በዘንድሮ  የሊጉ ጉዞአችሁ በጣም ጠንካራው  የነበረው ጎናችሁ ምን ነበር?

ጋቶች፦ በራሳችን በጣም እንተማመን ነበር። እያንዳንዱን ጨዋታም ለማሸነፍ  የነበረን መነሳሳት እና ፍላጎትም የሚገርም ነበር። ከዛ ውጪም  ይሄ ታሪካዊ ቡድን የሊጉን ዋንጫ ባልተለመደ መልኩ ካጣ ደግሞ አራት ዓመታትን ያስቆጠረ ስለነበር እና  ደጋፊውም ባለፉት አራት ዓመታት ጊዜ ውስጥ በቁጭት ስሜት ውስጥ  ስለነበር ከእዛ በመነሳት ጭምር  ነው  በሁሉም ነገር ማለትም   አንድነታችን፣  ህብረታችንና  የስነ-ልቦናው  ደረጃችንም ጥሩ ስለሆነም ጠንካራ  ጎናችን የነበረው።

ሊግ፦ ቅ/ጊዮርጊስ የሊጉን ዋንጫ ዘንድሮ ሲያነሳ እንደከዚህ ቀደም  ጥቂት ጨዋታዎች እየቀሩት አስቀድሞ አልነበረም፤ የዘንድሮ  ድሉንም  በመጨረሻ ቀን ላይ ነው ያሳካው፤ ይህ እንዴት ሊሆን ቻለ?

ጋቶች፦ በትክክል ብለሃል የሌላ ክለብ ተጨዋች በነበርኩበት ሰዓትም  ቡድኑ አስቀድሞ የሊጉን ዋንጫ እንደሚያነሳ አውቅ  ነበር፤ ዘንድሮም በእዛ መልኩ ሻምፒዮና መሆንን ፈልገን ነበር። ያም ሆኖ ግን በእግር ኳስ ጨዋታ ላይ እንዲህ ያሉ ነገሮች ስለሚያጋጥሙ የመጨረሻውን ቀን ለመጠበቅ በመገደድ ጣፋጩን ድል ልንጎናፀፍ ቻልን። ደግሞም በእዚህ መልኩ ከተከታይህ ክለብ ጋር በተቀራረበ ነጥብ እስከ ፍፃሜው ጨዋታ ድረስ ተጉዘህ ይህን የድል ስኬት ስታገኝም የደስታ ጣዕሙም  በጣም  ከፍ ያለ ስለሆነም  እኛም በእዛ መልኩ ነበር የተደሰትነው።

ሊግ፦ በቅ/ጊዮርጊስ  ክለብ  የዘንድሮው  የመጀመሪያ ዓመት ቆይታህ  ጥሩ እና አበረታች የሚባል ብቃትህን ለማሳየት ችለሃል፤ ይሄ አቋምህ ከእዚህ ቀደም ከተጫወትክበት እና ከፍተኛ እውቅና ካተረፍክበት ኢትዮጵያ ቡና የሚሻል እና ምርጥ

 

የሚባል ነው?

ጋቶች፦ የአሁኑ ምርጥነቱ በፕሪምየር ሊግ የሻምፒዮናነት ድል ጭምር የታጀበ ስለሆነ እንጂ ኢትዮጵያ ቡናም እያለው በእዚህ መልኩ ነበር ስንቀሳቀስ የነበረው። ያም ሆኖ  ግን ለአንድ ቡድን ስትጫወት ጥሩ መንቀሳቀስ ብቻ ዋጋ የለውም። የሊጉን ዋንጫ ለምትጫወትበት ክለብ ልታስገኝለት ይገባል። ያኔ ደግሞ የአንተ ስምም ጎልቶ ይጠራልና ወደ ቅ/ጊዮርጊስ ገብቼ ዋንጫ ማንሳቴና ጥሩ በመጫወቴም ነው የእኔን ብቃት በተለየ መልኩ ብዙዎቹ እንዲናገሩ ያደረጋቸው።

ሊግ፦ ጋቶች ፓኖም የዓመቱ የፕሪምየር ሊግ የኮከብ ተጨዋችነት ሽልማትን ዘንድሮ ይጠብቃል? /ከሽልማቱ በፊት ያቀረብንለት ጥያቄ ነበር/።

ጋቶች፦ አዎን፤ ቤትኪንጉ ላይ ጥሩ ተንቀሳቅሻለሁ፤ የኮከብ ተጨዋችነት ሽልማቱንም እጠብቃለሁ።

ሊግ፦ በቤትኪንግ ፕሪምየር ሊጉ የዓመቱ ኮከብ ተጨዋች ተብለሃል፤  ስለተሰማህ ስሜት እና ስለ ክብሩ የምትለን ነገር ካለ? /ከሽልማቱ በኋላ ያቀረብንለት ጥያቄ ነበር/።

ጋቶች፦ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ውስጥ ስትጫወት የወደፊት እልሞችህ እና ግቦችህ  ከሚሆኑት ነገሮች መካከል የሊግ ዋንጫን ከምትጫወትበት ክለብ ጋር ማንሳት፣ የሀገሪቱ ምርጥ ተጨዋች መባል ብሎም ደግሞ ለብሄራዊ ቡድን  መጫወት እና ወደ ውጪ ሀገር በመውጣትም በፕሮፌሽናል ተጨዋችነት መጫወት መቻል ዋንኞቹ መሆናቸው የሚታወቅ ሲሆን ለእኔ ያላሳካዋቸው ሁለት ነበሩ፤ አንዱ ዋንጫን ማንሳት ነበርና ያን አሳካው። ሌላው ደግሞ የዓመቱ የፕሪምየር ሊግ ኮከብ ተጨዋች ተብዬ ተሸለምኩ። በሐሙሱ ምሽት ፕሮግራም ላይ የእዚህ ክብር ባለቤት ስባል በጣም ነበር የተደሰትኩት። እንደ ዋንጫው ሁሉ ይህን ክብርም እፈልገው ነበር። አሁን ላይ ደስታዬ ልዩ ነው። ይህን የሽልማት ክብርንና  ከቡድኔ ጋርም ዋንጫን   ለማግኘት ዘንድሮ  ጠንክሬ ሰርቻለሁ። የኮከብነቱን ሽልማት ያገኘሁት ደግሞ በእኔ ብቻ ጥረት ሳይሆን በቡድን አጋር ጎደኞቼ፣ በኮቺንግ ስታፉ፣ በቤተሰቦቼ ከእኔ ጎን መሆንና ደጋፊዎቻችንም የሚሰጡኝ ማበረታታት እኔን በጣም ያነቃቃኝ ስለነበር የእነዚህ ድምር ውጤቶችም ናቸው ለክብሩ ያበቃኝና በቅድሚያ ፈጣሪዬን አስቀድሜ እነሱንም ላመሰግናቸው እፈልጋለሁ።

ሊግ፦ በቤትኪንግ ፕሪምየር ሊጉ ከቅ/ጊዮርጊስ ጋር ሻምፒዮና ከሆንክ በኋላ የቡድኑን መለያ እና የተሸለምከውን የወርቅ ሜዳሊያ ለአድናቂዎችህ ሰጠህ ወይንስ ራስህ ጋር አኖርከው?

ጋቶች፦ ይሄ የወርቅ ሜዳሊያ ሽልማት እኮ ታሪኩ ለእኔ ነው።  በእዚህ ጊዜም ከቅ/ጊዮርጊስ ጋር በቤትኪንግ ፕሪምየር ሊጉ ሻምፒዮና ሆኛለሁ ብዬም ለልጄ ወደፊት የምናገርበት ጊዜ አለና ለእዛም ነው ሜዳሊያውን ራሴ ጋር ያኖርኩት፤ ለእኔ ይህ የሻምፒዮንነት ክብር በእግር ኳስ ተጨዋችነት ዘመኔ ታሪኬ ውስጥም ልዩ ቦታ የምሰጠው ስለሆነም ሜዳሊያውን በክብር አስቀምጠዋል። የተጫወትኩበት መለያም ስኬትን ያስገኘልኝ ስለሆነም ከእኔው ከራሴ ጋር አብሮኝ ያለ ነው።

ሊግ፦ በቤትኪንግ ፕሪምየር ሊጉ የኢትዮጵያ ቡናው አቡበከር ናስር በዓምናው ውድድር ጎልቶ  በመውጣት የተለያዩ የኮከብና የክብር  ሽልማቶችን ሊወስድ ችሏል፤ በዘንድሮ ውድድር  አንተ ያው ኮከብ ተጨዋች ስለተባልክ ለአንተ ውጪ ለየት ብሎ የወጣው ተጨዋች ማን ነው?

ጋቶች፦ በጥሩ ተጨዋችነታቸው የተመለከትኳቸው ተጨዋቾች  አንድ ወይንም ደግሞ ሁለት ብቻ አይደሉም፤  ለኮከብ ግብ አግቢነት የተፎካከሩት ተጨዋቾች ሁሉ ለየት ባለ ብቃታቸው ሊቀርቡ ችለዋል። እንደዛም ሆኖ ግን ለአቡበከር ናስርና ለይገዙ ቦጋለ ቅድሚያን እሰጣለሁ። ይገዙ ደግሞ  ከጥሩ ተጨዋችነቱ ባሻገር የሊጉም ኮከብ ግብ አግቢ ተብሎ ስለተሸለመ በእዚህ አጋጣሚ እንኳን ደስ ያለህ ልለውም እወዳለሁ።

ሊግ፦  ከቅ/ጊዮርጊስ ጋር  በቀጣይነትስ ምን ነገሮችን ማሳካት ትፈልጋለህ?

ጋቶች፦ ለእዚህ ቡድን ስጫወት በአንድ ዋንጫ ብቻ ተወስኜ መቆየትን አልፈልግም ሌሎች ብዙ ላጣጥማቸው የምፈልጋቸው ስኬቶች አሉ። ከዛ ውጪም በአፍሪካ ክለቦች ሻምፒዮና ውድድር ላይም ቡድኑ የሚያልመውን ውጤት ማግኘትም ስለምፈልግ ይህን ስኬት ለመጎናፀፍ ሁሌም ጠንካራ ተጨዋች ሆኜ እቀርባለሁ።

ሊግ፦ ብዙ ጊዜ ከሌሎች ቡድኖች ወደ ቅ/ጊዮርጊስ የሚያመሩ ተጨዋቾች  በፍጥነት ከአዲሱ ቡድናቸው ጋር ለመላመድ ጊዜ  ሲወስድባቸው ይታይ ነበር፤ አንተ ግን በእዚህ በኩል አልተቸገርክም፤  የተለየ ምክንያት አለው?

ጋቶች፦ ወደ እዚህ ቡድን አምርቼ ከክለቡ ጋር በፍጥነት ልላመድ እና የውድድር ዘመኑም ኮከብ ተጨዋች ለመባል የቻልኩት በቅድሚያ በራሴ ልተማመን በመቻሌ እና  በስነ-ልቦናው ረገድም ጠንካራ ስለሆንኩኝ ነው። ቅ/ጊዮርጊስ ስትገባ ራስህን ለማውጣት ሁሌም ጠንክረህ መስራት እንጂ መፍራት የለብህም። ብዙ ተጨዋቾች እኮ ወደ ቡድኑ ሲመጡ የሻምፒዮናነትን ድልን ፈልገው ነው። ከእዚህ ያልተሻለ ውጤት ክለቡ ውስጥ ተቀባይነት ስለሌለው ሁሌም የራስ መተማመን ብቃትህን ልታሳድገው ይገባል።

ሊግ፦ ዋልያዎቹ በቅርቡ ግብፅን ያሸነፉበት የአፍሪካ ዋንጫ የማጣሪያ ጨዋታ በብዙዎች ዘንድ ተደንቋል፤ አንተም ጥሩ መንቀሳቀስህ ታይቷል። በእዚህ ዙሪያ እና ስለ ቡድናችን ለአፍሪካ ዋንጫ ማለፍ ዙሪያ አንድ ነገር በልና እናጠቃል?

ጋቶች፦ ከግብፅ ጋር ያደረግነው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ  ጨዋታ የእውነትም ምርጥ ነው፤ አሁንም ብዙዎቹ ስለዚያ ግጥሚያም  እያወሩም ነው። በዕለቱ የእኛ ቡድን ያን ግጥሚያ  ማሸነፍ መቻል ውድድሩ ላይ የሚቆይበትን ዕድል ስለሚፈጥርለት ለማሸነፍ ነበር ወደ ሜዳ የገባው። በዛ ላይ እኛ ጥሩ ሆነን ሳለ በማላዊ ብሄራዊ ቡድን የተሸነፍንበት አስቆጪ ውጤትም ስለነበር ከዛ በመነሳት ነው ራሳችንን በሁሉም መልኩ አዘጋጅተን ግብፅን ልንረታ የቻልነው። ይህ ውጤትም ለአፍሪካ ዋንጫው ለማለፍ ቀጣይ በሚደረጉት ጨዋታዎች ላይ የራሳችንን ዕድል በራሳችን እንድንወስንም ሁኔታዎችን ፈጥሮልናልና ለኮትዲቯሩ የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ የምንችለውን መስዋዕትነት ሁሉ የምንከፍልበትም ይሆናል።

spot_img
ተመሳሳይ ጽሁፎች

አስተያይት ያስፍሩ

እባክዎን አስተያይትዎን ያስፍሩ
እባክዎን ስምዎን እዚህ ያስገቡ

ትኩስ ዜናዎች

P