Free Porn
xbporn

buy twitter followers
uk escorts escort
liverpool escort
buy instagram followers
6x games unblocked fnaf unblocked games 76 unblocked games krunker.io slither unblocked io premium unblocked github.io unblocked games
Google search engine

“46 ሺህ ብር የነበረውን የነዳጅ ማደያ ኪራይ 905 ሺህ ብር በማድረሳችን መሸለም እንጂ መተቸት አይገባንም” “123 ሺህ ኳሶችን ከፊፋ ተረክበናል” አቶ ባህሩ ጥላሁን /የኢት እግርኳስ ፌዴሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ/

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጠቅላላ መደበኛ  ጉባኤና የማሟያ ምርጫ የፊታችን ሰኞ ይካሄዳል… የደቡብ ምዕራብ ፣ የትግራይና የአፋር ክልሎችም የሚወክሏቸውን አመራሮች ይመርጣሉ… ከሊጉ ዮሴፍ ከፈለኝ ጋር አጠር ያለ ቆይታ ያደረጉት የፌዴሬሽኑ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ባህሩ ጥላሁን ስለጠቅላላ ጉባኤው፣ 123 ሺህ ኳሶች ስለመጡበት የፌዴሬሽኑና ትምህርት ሚኒስቴር  ፕሮጀክት፣ ውዝግብ ስላስነሳው የማደያ ጨረታ ጉዳይና ስለፈዴሬሽኑ ህንጻ ስም ማዞር ዙሪያ ምላሻቸውን ሰጥተዋል….

ሊግ:- የማሟያ ምርጫና ጠቅላላ ጉባኤው ከነገ በስቲያ ሰኞ በአፍሪካ ህብረት አዳራሽ ይደረጋል.. እስቲ ስለሂደቱ እናውራ..?

ባህሩ:- አዎ ጉባኤው ይካሄዳል… ለኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ጠቅላላ ጉባኤ አባላት በመተዳደሪያ ደንቡ የጊዜ ገደብ መሰረት አስፈላጊው ሰነድና አጀንዳዎች ተልከዋል ፌዴሬሽኑ ህጋዊ በሆነ መንገድ ጉባኤው በሰላም እንዲጠናቀቅ ድጋፍ እያደረገ ነው፡፡ ክልሎች የወክሏቸውን አባላት የማጣራት ስራ ተሰርቷል፡፡ ጉባኤው ይካሄድበት የነበረው ኢሲኤ እየታደሰ በመሆኑ አሁን ጉባኤው የሚስተናገደው ሳር ቤት በሚገኘው የአፍሪካ ህብረት ነው፡፡ ከተቋሙ ጋር አስፈላጊውን ውል ተፈራርመናል፡፡ በዋናነት የማሟያ ምርጫ፣ ዕቅድ ሪፖርትና የውጪ ኦዲተር ሪፖርት ይቀርባል፡፡ ሶስተኛው ደግሞ ፌዴሬሽኑ ያዘጋጀው የጸደቀው ደንብ በፊፋ አጋዥነት የተለያዩ ስራዎች ስለተሰሩ እሱም ለአባላቱ ይቀርባል እንደ ፌዴሬሽን ጉባኤው በጥሩ ሁኔታ እንዲካሄድ ቅድመ ሁኔታው ተጠናቋል።

ሊግ:- ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር ያላችሁ ፕሮጀክት የት ደረሰ..?

ባህሩ:- አዎ ፌዴሬሽናችን ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመሆን ፕሮጀክት ቀርጾ ለፊፋ በማቅረብ ተቀባይነት አግኝቶ  በመጪው ህዳር ላይ ይፋ ይደረጋል፡፡ ለዚህም ፕሮጀክት የሚረዱ 123 ሺህ ኳሶች አዲስ አበባ ገብተው ተረክበናል፡፡ ኳሱ በሁለታችን በጋራ ወደ 60 ለሚጠጉና ለተመረጡ ትምህርት ቤቶች የሚሰጥ ይሆናል፡፡ ት/ቤቶች አካባቢ ያሉ የኳስ እጥረቶችን በተወሰነ መልኩ ይቀርፋል ብለን እናምናለን፡፡ ተማሪዎቹን የሚያሰለጥኑ አሰልጣኞችም ስልጠና ቀድመው የሚወስዱ ይሆናል፡፡ ይሄ ትልቅ ተግባር ነው፡፡ በዚህም ደስተኛ ነን፡፡ ከህዳር 13-15/2016  በሚኖረው ፕሮግራም ላይ የፌዴሬሽናችን እና የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮች የሚገኙ ይሆናል፡፡ ተሰናባቿ የፊፋ ዋና ጸሃፊ ማዳም ፋጢማ ሳሙራ የምትመጣ ይሆናል…

ሊግ:- የፌዴሬሽኑ ዋና ቢሮ የሚገኝበት ህንጻ አሁንም ስሙ አልዞረም እንዴ..?

ባህሩ:- ፌዴሬሽኑ የገዛውን ህንጻ ስም ማዞር ላይ ክፍተት እንደነበር የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ በተደጋጋሚ በጠቅላላ ጉባኤው ላይ የገለጹት ነው፡፡

ፌዴሬሽናችን ሻጩን ከሶት ያለበትን የመንግስትን ታክስ እንዲከፍል አድርጎ ስሙ ዞሯል፡፡ የሚገርመው ይፋ አላደረግነውም እንጂ ያለፈው ምርጫ በተጠናቀቀ በ20 ቀናት ውስጥ ካርታውን ተረክበን ስሙ በኛ ዞሯል፡፡ ዝም ብሎ ወሬ እንጂ አሁን ይሄ ገዳይ መሆኑ ቀርቷል…

ሊግ:-  የነዳጅ ማደያው ጨረታ ላይ የተሰራው ስራ ህጋዊ መስመርን የተከተለ አይደለም የሚሉ  አሉ… የናንተ ምላሽ ምንድነው …?

ባህሩ:- ስታዲየም አካባቢ ከቀይ መስቀል ፊትለፊት ያለው ኦይል ሊቢያ ሲከራይ የነበረው 46 ሺህ ብር ነበር፡፡ ይኧው ተከራይ በራሱ ምክንያት አቋርጧል፡፡ ፌዴሬሽኑም ጨረታ በማውጣት ወደ 9 የሚጠጉ አካላት ተወዳድረዋል፡፡  የፌዴሬሽኑ የጨረታ ኮሚቴ ፌዴሬሽኑ የተሻለ ገንዘብ እንዲያገኝ በሚያስችል አትኩሮት አራት ተወዳዳሪዎችን መረጠ፡፡  በዚህም 630 ሺህ ብር ያቀረበ አለ፡፡ አንደኛው ወደ 500 ሺህ ብር አካባቢ ሁለት ተወዳዳሪዎች 400 ሺህ ብር አቀረቡ፡፡ እስከ መቶ ሺህ ያቀረቡ አሉ፡፡ በተመሳሳይ ደግሞ የቴክኒካል ነገሩን እንዲያይ ለኦይል ሊቢያ ላክን፡፡ እነሱም መርምረው አይተው ወደ አራት ተወዳዳሪዎችን መርጠው ላኩ… ቴክኒካልና ፋይናንሺያል ጥናት አድርገው ኢንተርቪው  አድርገዋቸው ከ100 70 ፐርሰንትና ከዚያ በላይ ያመጡትን ነው የላኩልን… በነሱ ውጤት የመጀመሪያው ሰው 630 ሺህ ብር በወር እከፍላለሁ ያለው ነው፡፡ በደረጃ ተመርጠው የመጡት እስከ 400 ሺህ በወር እንከፍላለን ያሉትን ነው… ከዚህ ውሳኔ በኋላ ይሄ አይን ቦታ ነው ያስጨምራል ለምን በድርድር አናወራቸውም አልንና ጨረታውን ውድቅ አደረግን፡፡

ሊግ:- ሃሳባችሁ ግን ተሳካ..?

ባህሩ:- አዎ ውሳኔውን ለማኔጅመንት ኮሚቴ አቀረብኩና አሪፍ አሳብ መሆኑ ከተማመንን በኋላ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ የመሠረዝ መብታችንን ተጠቅመን ውድቅ አደረግን… ከዚያም ሂደቱን ከጨረታ ኮሚቴ ወደ ማኔጅመንት ኮሚቴ ወስድኩት፡፡ ማኔጅመንት ኮሚቴው የፌዴሬሽኑ ዳይሬክተሮች ብቻ ያሉበት ኮሚቴ ነው፡፡ በድርድሩ አራቱን ኦይል ሊቢያ የመረጣቸውን ወገኖች ለማናገር ወሰንን..

ሊግ:- ሌሎቹ ተሳታፊዎቹን በድርድሩ ውስጥ አላካተታችኋቸውም ..?

ባህሩ:- አዎ ለስፖርቱ ቅርበት አላቸውም ብለን ለማካተት አስበን ነበር፡፡ ነገር ግን የኦይል ሊቢያ ይሁንታ ያገኙትን ብቻ መሆን አለበት የሚለው ሃሳብ አሸነፈና ከአራቱ ጋር ተደራደርን… ለድርድሩ እንደ ኮሚቴ አዋቅሬ አንዳንድ ተወዳዳሪ ብቻ እንዲያናግሩ አድርጌ በጋራ ደግሞ የአራቱም እኩል በፊት ለፊታቸው እንዲከፈት ተደረገ.. መጀመሪያ 630 ሺህ አቅርቦ የነበረው 756 ሺህ ብር አቀረበ 400 ካቀረቡት መሃል አንዱ 905 ሺህ ብር አቀረበ፡፡ የአመቱንም በቅድሚያ እከፍላለሁ በማለቱ ተስማማን፡፡ የሚጠቅመንን የመወሰን መብቱ ደግሞ የኛ በመሆኑ ጨረታው እንዲህ ተካሂዶ ተጠናቀቀ፡፡ ለህጋዊነቱ ምንም አይነት ክፍተት የለም ሌላው ወሬ አይመለከተንም፡፡

46 ሺህ ብር የነበረውን የማደያ ኪራይ 905 ሺህ ብር በማድረሳችን መሸለም እንጂ መተቸት አይገባንም ይሄንን ነው ማለት የምችለው…

ሊግ:- ጨረስኩ…የመጨረሻ የምትለው ካለ…?

ባህሩ:- ጠቅላላ ጉባኤውን በፊፊና በካፍ የጉባኤ ስታንዳርድ ደረጃ ለማድረግ ሞክረናል… በተቻለ መጠን በሰላም እንዲካሄድ ስራውን ሰርተናል፡፡ የተሳካ ጉባኤ ለኢትዮጵያ እግር ኳስ የሚጠቅም ሃሳብ የሚነሳበት ጉባኤ እንዲሆን እመኛለሁ፡፡

ሊግ:- አመሰግናለሁ….

spot_img
ተመሳሳይ ጽሁፎች

ትኩስ ዜናዎች

P